Loading Events
  • This event has passed.
 የታሪክና የጥበብ ውህደት፡ “አክሊሉ” የታሪካዊ ልብ-ወለድ መጽሐፍ ምርቃት!
ታሪክን ከፈጠራ ጥበብ ጋር አዋህዳ በልዩ ሁኔታ የከተበችው ደራሲ ዶ/ር ሰላማዊት ታደሰ“አክሊሉ” የተሰኘውን አዲስ ታሪካዊ ልብ-ወለድ  መጽሐፏን ለንባብ ልታበቃ ነው።
ይህ በጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ የሕይወት ታሪክ ላይ ተመርኩዞ የተጻፈው ድንቅ ልብ-ወለድ፣ የኢትዮጵያን የታሪክ ክስተቶች በልዩ የጥበብ ቀለም ስሎ ያቀርብላችኋል!
 በዕለቱ የሚገኙ የክብር እንግዶች፡

ቴዎድሮስ አጥላው፦ ደራሲና ሐያሲ

ዋሊሁን በላይ፦ አርቲስት

የምረቃው መርሐ-ግብር፦

ቀን፦ ነገ ቅዳሜ መጋቢት 05 ቀን 2018 ዓ.ም.

ሰዓት፦ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ

ቦታ፦ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት (ወመዘክር)

የታሪክን እውነት ከልብ-ወለድ ጣዕም ጋር አጣጥሞ ለመቋደስ ነገ በወመዘክር እንገናኝ!

Location

Location
The National Library (ወመዘክር-Wemezekir)
Address
https://maps.app.goo.gl/BWbJsaXCh5pED5tE6?g_st=ac
Addis Ababa, Ethiopia

Leave a Reply

AddisBooks Ads