Loading Events
🌟 የመፅሐፍ ምረቃ ጥሪ 🌟
“ለምን?”  የለውጥ መጀመሪያ ጥያቄ !
በደራሲ አዱኛ ሂርጳ የተፃፈውና “አለመቻልን የምትፋለመው ትንሿ ጠጠር” በሚል ንዑስ ርዕስ የሚታወቀው “ለምን?” የተሰኘው አዲስ መፅሐፍ የፊታችን ቅዳሜ በድምቀት ይመረቃል። የዚህ ልዩ መርሀ ግብር አካል እንዲሆኑ ተጋብዘዋል።
📅 ቀን፦ ቅዳሜ፣ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

🕙 ሰዓት፦ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ

📍 ቦታ፦ ወዳጅነት ፓርክ (Friendship Park)፣ አዲስ አበባ
በዕለቱ የሚጠበቁ የክብር እንግዶች እና ተናጋሪዎች፦
  • ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰሎሞን
  • አቶ ሺፈራው ወልደሚካኤል (የቀድሞ የፍትህ ሚኒስትር)
  • ዶክተር ምህረት ደበበ
  • አቶ ክብረት አበበ (የጠብታ አምቡላንስ መሥራች)
የመፅሐፍ ቅኝት የሚያቀርቡ፦
  • ቢንያም አቡራ
  • ደራሲ መሐመድ አል ቡርሀን
የመድረክ አጋፋሪ፦
  • ገጣሚ ረድኤት ተረፈ
የጥበብና የእውቀት ማዕድ በሆነው በዚህ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በመገኘት የደራሲውን አዲስ ስራ አብረን እንመርቃለን።

Location

Location
Friendship Park
Address
https://maps.app.goo.gl/e97qb639hkuatP1v9
Addis Ababa, Ethiopia

Leave a Reply