Loading Events
 የክብር ግብዣ፡ “የቼቼላው አባታችን” የመጽሐፍ ምረቃ!
ለግማሽ ክፍለ ዘመን (ለ52 ዓመታት) በሕክምናው ዘርፍ በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል፣ አያሌ ፕሮፌሰሮችንና ዶክተሮችን ያፈሩት የኢትዮጵያ ባለውለታ ፕ/ር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ አሁን በታተመ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል።
በአስተባባሪ ኮሚቴዎች እገዛ፣ በታታሪው ደራሲ ዶ/ር ሰሎሞን በርሄ የተሰናዳውና የባለውለታውን አሻራ የሚዘክረው ❝የቼቼላው አባታችን❞ የተሰኘው መጽሐፍ በደመቀ ሁኔታ ይመረቃል።

በዕለቱ የሚገኙ የክብር እንግዶች፦

ፕሮፌሰር ማለ ማሩ (የመጽሐፉ ባለታሪክ)

ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ (ተናጋሪ)

ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ (ተናጋሪ)

ዶ/ር ሰሎሞን በርሄ (የመጽሐፉ ደራሲ)

የመጽሐፉ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት

የምረቃው መርሃ-ግብር፦

ቀን፦ ቅዳሜ፣ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

ሰዓት፦ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ

ቦታ፦ ቀበና አደባባይ በሚገኘው የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ማህበር (EPHA) አዳራሽ

ታላላቅ የሕክምና ባለሙያዎች፣ የሀገር ባለውለታዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሚገኙበት በዚህ ታሪካዊ መርሃ-ግብር ላይ እንዲገኙ በክብር ተጋብዘዋል።
መግቢያው በነጻ ነው!
ኢትዮጵያ ባለውለታዎቿን ታከብራለች! በዕለቱ እንገናኝ።

Location

Location
EPHA
Address
https://share.google/kmrcuLtZZ6SVTWEkY
Addis Ababa, Addis Ababa Ethiopia

Leave a Reply

AddisBooks Ads