ወሪሳ (የውድቀት ፈለጎች) Werisa (Yewidket Felegoch)
Werisa (Yewidket Felegoch) (Paper Cover) ወሪሳ (የውድቀት ፈለጎች) By Alemayehu Gelagay
አንድ የአማርኛ መምህር ከአርሲ ነገሌ በሰራ ቅያሪ አዲስ አበባ ወደምትገኝ ወሪሳ በምትባል ሰፈር አክስቱ ለጊዜው ወዳወረሱት ቤት ይገባል:: መምህሩ በዚህች ሰፈር እንዲሁም በጎረቤት ሰፈሯ "እሪ በከንቱ" የሚያጋጥመውን የመላመድና የመኖር ፈተና ፣ ግጭት ፣ መስማማት ፣ ተንኮል ፣ ፍቅር ፣ አጣብቂኝ ፣ ውዝግብ ፣ እንዲሁም የሚሰማቸውን ወግና ታሪክ(ተረት) ይተርካል::
መፅሐፉ የሚያነሳችው ወጎች ፣ ተረትና ምሳሌዎች ፣ ታሪኮች(ተረቶች) ተምሳሌያዊነትን ያዘሉ ሲሆን የኢትዮጵያን ያለፈ እና የአሁኑን ታሪክ: የአሁኑ ትውልድ የሚያይበትን የተዛባ ዓይን ፣ በአሁኑ ትውልድ ውስጥ ስላሉት የተለያዩ ነባራዊ ሐቆች እንዲሁም ልዩነት ያላቸው ተጎራባቾች ላለፈው ታሪክ የሚያድርጉትን ሽሚያ እና ሽኩቻን ያሳያል::
$5.99
አልተዘዋወረችም Altezewawerechim
ፍቅር ሁሉ ፍቅር አይደለም። በደፈናው አፈቀርን ወይም ተፈቀርን እንበል እንጅ ሰዎች ምናችንን በምን ምክንያት እንደወደዱልን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻል ነገር አይደለም። ሰዎች ከማንነት በላይ ለአካላዊ ውበት በፍቅር ሊወድቁ ይችላሉ፤ ምናልባትም ይህ ለራሳቸውም አይገባቸውም ይሆናል። ከነጭራሹ «ወደድናችሁ» ያሉን ሰዎች እንደወደዱን ማረጋገጫችንስ ምንድነው ? ትዳር ? ስጦታ? ቃልኪዳን? ለእኛ የሚከፍሉት መስዋዕትነት? በመኖር ብቻ የሚመለስ ጥያቄ ሳይሆን አይቀርም። በዚህ መፅሐፍ ከነመኖራቸው ትዝ የማይሉን ጥቃቅን ስሜቶች ስንጥቃቸው እየሰፋ ሕይዎትን ለከባድ ምስቅልቅል ሲዳርጉ እናያለን። «ምናለበት» ተብለው ችላ የተባሉ እንደውም እንደበጎ ነገር የሚታዩ ጉዳዮች በጥልቀት ሲቃኙ ያላቸውን አደገኛ ስር እንመለከታለን። በሕይዎት ውስጥ « ቁጭ ብለን የሰቀልነውን ቁመን ማውረድ ሲያቅተን» ሌሎች ድሎት ያሉት ነገር ለሌላው መከራ ሲሆኑ ፣ እንታዘባለን። ፅናት፣ ፍቅር ፣ ስደት ፣ናፍቆት ፣ዓላማ ፣ ሐዘን ፣ደስታ ፣ በውብ ትረካ ተሰድረው እናገኛቸዋለን። እንደቀላል የልጅነት ሁዳዳችን ላይ የተጣለች ቅንጣት የቃል ዘር በኋለኛው ዘመናችን ዛፍ ሁና ጥላዋን በአኗኗራችን ላይ ስታጠላ እንታዘባለን። በመጨረሻም መፅሐፉን ስንከድን የራሳችንን ሕይወት ከፍተን መመልከት እንጀምራለን።
$5.99
ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት
ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት በዓለማየሁ ገላጋይ
The life of Sebhat Gebre-Egziabher and his skills book by Alemayehu Gelagay
የዓለማየሁ ገላጋይ ሥራዎች:
"ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት"፣ "ቅበላ"፣ "የብርሃን ፈለጎች"፣ "ኢህአዴግን እከሳለሁ"፣ "ኩርቢት"፣ "ወሪሳ"፣ "አጥቢያ"፣ "የፍልስፍና አፅናፍ"፣ "በፍቅር ስም"፣ "መለያየት ሞት ነው"፣ "በእውነት ስም (ታለ)"፣ "ውልብታ"፣ "በእምነት ሥም(ሐሰተኛው)"፣ "የተጠላው እንዳልተጠላ" "ቤባኒያ (ዕውነት ሐሰት)"፣ "ማዕበል ጠሪ ወፍ"፣ የተሰኙ ልቦለድና ኢልቦለድ መፃሕፍት ለአንባቢያን አበርክቷል። ከዚህ በተጨማሪም "መልክዓ–ስብሐት" በተሰኘው መጽሐፍ 27 ጸሐፊያን፣ ደራሲያን፣ ገጣሚያንና ሰዓሊያን አሳትፎ በማሰናዳት ለአንባብያን አድርሷል።
$5.99
የብርሃን ፈለጎች Yebirhan Felegoch
ማጀቱን ቸል ብሎ የሰፈሩን መንገዶች ለማሰስ የደፈረ ሕጻን፣ ጎርምስና ሲያጣድፈው ጣፋጭና ጎምዛዛ ሕይወት እየዛቀ ሲበትን፣ ሳያውቀው የብይትውርናን በር ያንኳኳል፡፡ በብርሃን ፈለጎች ብርሃን የተነፈጉና ጭላንጭሉ ያጓጓቸው ገጸ ባህሪያት ተመልምለዋል፡፡ ጥቂት ናቸው፤ በለጋ እድሜያቸው የኑዛዜ ዕቃ ተረካቢ ይመስል የሕይወትን ጓዳ የሚበረብሩ፣ ዓለማየሁ ገላጋይ በግንብ ተከልለው ለሚነቅዙት ሳይሆን በየሜዳው ኳስና ኑሮን ለሚጠልዙት ነው ያደላው፡፡ በአጥቢያ፣ ቅበላና፣ ኩርቢት ኮስታራ ጭብጦችን የፈለቀቀው ደራሲ በየብርሃን ፈለጎች ለትልቅ ጉዳይ ሳይሆን ከውስጣዊ ጉዞ በመዝመት ልቦናን፣ ዕምነትን በቅኔያዊ ቋንቋ አወርዝቶ፣ ለፍቅር፣ ለድልና ሽንፈት ያቃስታል፡፡
$9.99
Addis Hiwot by Dagmawi Assefa
አዲስ ሕይወት በዳግማዊ አሰፋ Addis Hiwot - A book by Dagmawi Assefa.
Addis Books
Kemaizenu Wedih by Dagmawi Assefa
ከማዕዘኑ ወዲህ በዳግማዊ አሰፋ Kemaizenu Wedih by Dagmawi Assefa
Addis Books
በምሥራቅ በኩል By Solomon Sahele Tizazu
በምሥራቅ በኩል Be Misrak Bekul a book By Solomon Sahele Tizazu.
ዋጋ: 500 ብር
በሚከተሉት የባንክ አካውንቶች ይጠቀሙ: በአድራሻዎ ይደርስዎታል::
1000025047447 CBE
ሰለሞን ሳኅለ (ሶል) በግጥሞቹ ነፍሳችንን ሲያባባ፣ በአጫጭር ልቦለዶቹና በወጎቹ ደግሞ ስሜታችንን ሲገዛ ቆይቷል። አሁን ግን ረዥም፣ ዝርው እና እውነተኛ ታሪክን መሠረት ባደረገው “በምሥራቅ በኩል” በተሰኘ አዲስ ሥራው ብቅ ብሏል። ሶል ወደ አዲሱ የጽሕፈት ዘውግ ሲሻገር ማየት ለሁላችንም ትልቅ ጉጉት ነው።
$10.00
የማታ እንጀራ በዓለም ፀሐይ ወዳጆ Yemata Injera Alemtsehay Wedajo
የማታ እንጀራ በዓለም ፀሐይ ወዳጆ (Yemata Injera book by Alemtsehay Wedajo)
አቅሜ ትዝብቶችን በስንኝ ቆጣጥሮ መዋል ማደር ነውና የማደንቀውንም የምወቅሰውንም ከትቤአለሁ፡፡ ተፈጥሮን . . . ውበትን ለመዳሰስ ሞክሬአለሁ፡፡ ዓርማዎቼን በሙገሣ ሳሽር የወገንን ችግርና ብሶት በመዳሰስ በተለይም በበቀሉበት በቅሎ ሳይመረት የሚሠፈረውንም ዘልፌአለሁ፡፡ ወድጄም አይደል! በሌላ በኩል እየሞቱ ለኖሩ አድናቆትን፣ እያሉ ለሞቱትም ትንሽ ዘራፍነትን ለመቸር ሞክሬአለሁ፡፡ የግጥም ዋይታዬ ወገንን በህብረት አጠንክሮ ተስፋን አጭሮ ለውጤት የሚረዳ ይሁንልኝ፡፡
$10.00
ከዕለታት ግማሽ ቀን KE ELETAT GIMASH QEN
Alex Abraham is one of the most influential young voices in modern Amharic literature. His bestselling books have earned wide acclaim for their powerful exploration of love, injustice, and social change, blending Ethiopian tradition with contemporary storytelling.
"ከዕለታት ግማሽ ቀን" /Ke eletate Gmash Ken/his fifth book, continues this journey—offering a sharp, compelling look at the human experience and the challenges shaping society today.
$15.00

















