Cart

Authors

  • Home

ሳባ ሲሳይ Saba Sisay

በመተሐራ ስኳር ፋብሪካ /መርቲ/ ተወልዳ ያደገችው ገጣሚት ሳባ ሲሳይ ገና በልጅነት ዕድሜዋ የጽሑፍ ዝንባሌዋን ተረድታ በአዳማ /ናዝሬት/ ከተማ በሚገኙ የኪነ ጥበብ ቡድኖች ውስጥ የመጀመሪያ ልምምዷን የጀመረች ሲሆን በቀጣይ ራሷን ወደከፍተኛ

Author's Books

Deciding What to Read Next?

Description

በመተሐራ ስኳር ፋብሪካ /መርቲ/ ተወልዳ ያደገችው ገጣሚት ሳባ ሲሳይ ገና በልጅነት ዕድሜዋ የጽሑፍ ዝንባሌዋን ተረድታ በአዳማ /ናዝሬት/ ከተማ በሚገኙ የኪነ ጥበብ ቡድኖች ውስጥ የመጀመሪያ ልምምዷን የጀመረች ሲሆን በቀጣይ ራሷን ወደከፍተኛ ትምህርት በማሳደግ የቲያትር ጥበብ ትምህርትን የመከታተል እንዲሁም አ.አ ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከልን ጨምሮ በበርካታ መድረኮች ስራዋን የማቅረብ ዕድል ነበራት ። በወቅቱ ባጋጠማት የጤና እክል ምክንያት ግቧን ሳትፈጽም ወደናዝሬት ከተማ ተጉዛ የልብስ ፋሽን ዲዛይነር በመሆን ለዓመታት በዘርፉ ላይ ሰርታለች.

የነፍስ ጥሪዬ ጽሑፍ ነው በማለት ከረዥም ጊዜ በዃላ “የብርሃን ጥሞና” የተሰኘ የግጥም መድበል ለአንባቢ ያደረሰች ሲሆን በአጭር ጊዜ ተቀባይነትንና ተወዳጅነትን ያገኘ ስራ ተብሎላታል ይህ የግጥም መድበል የገጣሚቷን የሕይወት ፍልስፍናና የመረዳት ክህሎት ከመግለጹም ባሻገር በቀጣይም በሌሎች የስነ-ጽሁፍ ዘርፎች እንደምትመጣ የጠቆመችበት ነው።

Review

Customer Reviews

Write A Review

AddisBooks Ads