የአሸናፊነት ጉዞ Ye Ashenafinet Guzo by Dr Shimelis Wondimu
$9.99
The Weight of Salvation by Dr Shimelis Wondimu.
Addis Books!
Description
by Dr Shimelis Wondimu
የእግዚአብሔር ዘላለማዊ አሳብ መጽሐፍ ቅዱስ በዘፍ 1፡1 ላይ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ በማለት ይጀምራል፤
በፍጥረት ሂደት ሰማይና ምድር የመጀመሪያውን ቦታ ይይዛሉ፤ በመቀጠል ብርሃንና ጨለማን ለይቶ ብርሃኑን ቀን ጨለማውን
ደግሞ ሌሊት ብሎ ብርሃንንና ጨለማን ሲለይም ሆነ በተጨማሪ በውሆች መካከል ጠፈር ይሁን ብሎ በውኃና በውኃ መካከል
ከፍሎ፤ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትን ውኆች ሲለይ፤እንዲሁም ከጠፈር ወይም ከሰማይ በታች ያለውን ውኃ በአንድ
ስፍራ ይሰብሰብ ብሎ፤ የብሱ ወይም መሬቱ ይገለጥ ብሎ ቦታ ቦታቸውን ሲያሲዛቸው እናነባለን። በምድር ላይ የተለያዩ
ዕፅዋት እንዲበቅሉ ማድረጉን፣ በተጨማሪም እንደየወገኑ ሁሉን ሰብስቦ፤የአፈጣጠርና የቦታ ድልድል መስጠቱን መጽሐፉ
ያስረዳል። ቀንና ሌሊትን እንዲለዩ ሁለት ታላላቅ ብርሃናትን ፈጥሮ ትልቁን በቀን ትንሹን ደግሞ በሌሊት እንዲሰለጥኑ
አድርጎ ዘመናትም በእነዚህ ብርሃናት እንዲለዩ ሲያደርግ ዘላለማዊ አሳቡ ያ ብቻ አልነበረም። ነፍስ ያላቸው ተንቀሳቃሾች
ሁሉ፤ በቃሉ አማካኝነት ከውኃ እንዲፈጠሩ ሲያደርግም የእግዚአብሔር የዘላለም አሳቡ ያ ብቻ እንዳልነበር እናስተውላለን።
Reviews (0)
You must be logged in to post a review.
AddisBooks Ads








Reviews
There are no reviews yet.